DBE Holds its 3rd Quarter Meeting via Video Conference
Development Bank of Ethiopia /DBE/ held the first ever video conference its Third Quarter Management Meeting in using Zoom platform on May 15 & 16, 2020 aims to prevent the wide-spreading of Corona Virus (COVID-19).
During the two days meeting, performance report of the Bank in all districts and at the corporate level was presented and important discussion was held over by management members of the Bank.
The report covered credit operations, the change related activities, financial, HR and other function’s performance of the Bank for the third quarter and nine months, problems encountered, corrective measures taken, strengths and weaknesses assessed and the way forward.
While chairing the meeting, President of the Bank, Ato Haileyesus Bekele said from this online meeting and discussion, significant inputs will be gathered for the next year plan preparation.
According to the report presented, the credit operations performance of the Bank for this quarter is better than that of the previous year same period. Overall, the Bank registers satisfactory level performance by approving birr 2.3 billion, disbursement of birr 2.2 billion and collection of birr 2.16 billion both in project and lease financing.
The Bank also sold Grand Renaissance Bond amounted to birr 133.7 million during the quarter.
Finally, Ato Haileyesus Bekele said despite many challenges facing such as COVID-19 pandemic, we should work hard in smarter way to achieve set targets by reducing of NPLs, increasing the volume of bond sales, and loan collection.
ባንኩ ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 5 ሚሊዮን ብር በስጦታ አበረከተ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ብር 5 ሚሊዮን መጋቢት 25 ቀን 2012 ዓ.ም. በስጦታ አበርክቷል፡፡
ባንኩ የገንዘብ ስጦታውን ያበረከተው በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ነው፡፡
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ የቦንድ ስጦታውን ለጽ/ቤቱ ካስረከቡ በኋላ ባደረጉት ንግግር ባንኩ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ቦንድ በማቅረብ፣ ሽያጩን በማስተባበር እና በማስተዳደር አስተዋጽዖ እያደረገ እንደሚገኝ፣ ይህንኑ ጉልህ አስተዋጽዖ በማጠናከር በዛሬው እለትም ባንኩ ለግድቡ ግንባታ የሚውል 5 ሚሊዮን ብር በስጦታ ማበርከቱን እና ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስም አስተዋጽዖው እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
አቶ ኃይለየሱስ ከዚህ ቀደም መላው የባንኩ ሠራተኛ ሁለት ዙር የቦንድ ግዥ መፈጸሙን አስታውሰው አሁንም ግንባር ቀደም መሪ እና አርአያ በመሆን የባንኩ ማኔጅመንት የቦንድ ግዥ ለመፈጸም መወሰኑን ተናግረው፣ መላው ሠራተኛም ይህንኑ አርአያ እንዲከተል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በመቀጠል የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሮማን ገብረሥላሴ በበኩላቸው ባንኩ ለግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ላበረከተው የ5 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ስጦታ አመስግነው ሌሎች መሰል የፋይናንስ ተቋማትም የባንኩን አርአያ በመከተል ዋናው ጤና ስለሆነ ጤናን በመጠበቅ አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ባንኩ ለግድቡ ግንባታ ካበረከተው አስተዋጽዖ በተጨማሪ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት በአገራችን እንዳይስፋፋ በሃገር አቀፍ ደረጃ ለሚደረገው ጥረት የ5 ሚሊዮን ብር ልገሳ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ባንኩ ለኮሮና ቫይረስ ሥርጭት መከላከል 5 ሚሊዮን ብር ለገሰ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሃገር አቀፍ ደረጃ የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ሥርጭትን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ብር 5 ሚሊዮን ድጋፍ አደረገ፡፡
ባንኩ የገንዘብ ድጋፉን ያደረገው መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ሠላም ሚኒስቴር በሚገኘው የኮቪድ-19 ብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ነው፡፡
የባንኩ ፕሬዚዳንት ተወካይ እና ም/ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ዋቄ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት ይህን ሥርጭት ለመከላከል ከምንጊዜውም በላይ መደጋገፍ ያስፈልጋል፤ ይህ በሽታ ማንን እንደሚያጠቃ አይታወቅም፤ ይህን ድጋፍ ስናደርግ ለራሳችን እና ለምንወዳቸው ጭምር በማሰብ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ መተጋገዝና እና መረዳዳት ያስፈልጋል ብለዋል፤ በተለይም በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ ለተሰማሩ የባንኩ ደንበኞች ሠራተኞቻቸውን በአግባቡ እንዲይዙና እንዲንከባከቡ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
የኮቪድ-19 ብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋ በበኩላቸው ይህን ፈታኝ ጊዜ እኛው ለእኛው፣ ኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን ሆነን አገርና ዜጋ በማዳን መሻገር ይኖርብናል ያሉ ሲሆን፤ በዚህ አገርንና ዜጋን የማዳን ጥረት የገንዘብ ድጋፍ ላበረከቱ ተቋማት በመንግስት ሥም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡
በእለቱ የኢትዮጵያ ልማት ባንክን አስተዋጽዖ ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማት ብር 47 ሚሊዮን ለመሰብሰብ እንደተቻለ ታውቋል፡፡
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የቦንድ ሽያጭ ሣምንት በይፋ ተከፈተ
ከመጋቢት 15 እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የሚካሄደው ሀገር አቀፍ የቦንድ ሽያጭ ሣምንት “ጤናችን ይጠበቃል፤ ግድባችን ይጠናቀቃል” በሚል መሪ ቃል መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም. በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል በይፋ ተከፍቷል፡፡ ጋዜጣዊ መግለጫም ተሰጥቷል፡፡
በመክፈቻው እለት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ ወ/ሮ ሮማን ገ/ሥላሴ እና እና የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዝዳንትና የጽህፈት ቤቱ አባል ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ተገኝተዋል፡፡
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ ግድቡ የታሰበለትን ዓላማ እንዲያሳካ እና እስኪጠናቀቅ ድረስ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ እና ለዚህም በሁሉም ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች ቦንዱን ለመሸጥ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡
በዚህ መርኃ ግብር 500 ሚሊየን ብር ለማሰባሰብ እቅድ መያዙንም ወ/ሮ ሮማን ገብረ ሥላሴ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ በበኩላቸው ለግድቡ ፍጻሜ የህብረተሰቡ ድጋፍ ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የቦንድ ሽያጭ ሣምንቱ በይፋ መከፈቱ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ለማነቃቃት የሚረዳ በመሆኑ መገናኛ ብዙኃን በበኩላቸው የተጀመረውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከዳር ለማድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ የቦንድ ግዥው ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በመግለጫው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ በፊት ቦንድ የገዙና የመውሰጃ ጊዜያቸው የደረሰ ካሉም ጊዜውን እንዲያራዝሙ፤ ትላልቅ ድርጅቶችም ከዚህ ቀደም ያደርጉት የነበረውን ልገሳና የቦንድ ግዥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ እና በአሁኑ ጊዜም 71% የደረሰውን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ በመግለጫው ወቅት መልእክት ተላልፏል፡፡
Page 25 of 31