Awareness Raising Workshop on ALMP Held
An awareness raising workshop held for successful suppliers who passes Agricultural Mechanization Leasing Project (ALMP) supplier due diligence requirement of the Bank at the Head Office on October 21, 2021.
The workshop was provided by expertise’s who came from GFA Consulting Group.
Opening the speech, A/Vice President, Small & Medium Enterprises Financing, Ato Abiot Daida said that the prime objective of this workshop is to create common understanding with stakeholders through awareness raising program. He said, and adding that this workshop will be taken as one of the requirements enables to implement Agricultural Mechanization Leasing Project with the Bank.
The successful suppliers, namely, Hagbes PLC, Moenco Ethiopia, Adeb Engineering & Trading PLC, ALT Agricultural Equipment Importers, Ethiopian Agricultural Business Corporation, Kaleb Service Farmers House PLC, Ultimate Motors PLC were in attendance in the workshop.
Finally, cooperation agreement was signed between the Bank and the successful suppliers.
ባንኩ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የቤት እድሳት ፕሮግራም አስጀመረ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቂርቆስ እና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ 11 የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤቶችን እና 1 መጸዳጃ ቤት የዕድሳት ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ነሐሴ 18 እና 19 ቀን 2013 ዓ.ም አከናውኗል፡፡
የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ለዕድሳት ሥራው ሲፈርስ
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት የተከበሩ ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ)፣ የባንኩ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የሥራ መሪዎች፣ የየክፍለ ከተሞቹ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የወረዳ አመራሮች፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ለቤት ዕድሳት የተመረጡትን ቤቶች የማፍረስና እድሳቱ በማስጀመር ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው (ፒ.ኤች.ዲ) ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ተግባራዊ የሚደረጉ ፕሮጀክቶች በዋናነት እንዲያካትቷቸው ከሚገደዱባቸው መሥፈርቶችም አንዱ ማኅበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደመሆኑ ባንካችን ለሀገር ዋጋ የከፈሉትን ማሰብና ለሀገራቸው የዋሉት ውለታ በከንቱ እንዳልነበር ማስታወስ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ግዴታም ነው ብሎ የሚያምን በመሆኑ በዚህ የቤት ዕድሳት መርኃ ግብር ላይ ተሳታፊ ሆኗል ብለዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ለሀገር ውለታ በመዋል ስሌት የዕድሜ ጠገብ አረጋውያን ያህል መታወስና መመስገን ያለበት አካል የለም ያሉ ሲሆን፤ አያይዘውም ባንካችን የአረጋውያንን እና አቅመ ደካሞችን ቤት ለማደስ ያደረገው ድጋፍ ባንኩ ለሀገር ባለውለታ አረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ያለውን ትኩረት ማሳያ ጅምር ሥራ መሆኑን፣ ሀገር የህልውና አደጋ ላይ ስትሆን ደግሞ ባንኩ ሀገራዊ ጥሪዎችንም በመቀበል ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲሁ ከ96 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸው፤ ለወደፊቱም ይህን ተልዕኮ አጠናክሮ በመርህና በዕቅድ ስለሚሠራ ባንኩ ለሚሠራው ሥራ ሁሉ ሁሉም አካላት ተባባሪ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አባወይ ዮሐንስ እና የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተጫነ አዱኛ በበኩላቸው ባንኩ ከልማት ሥራዎቹ ጎን ለጎን የአቅመ ደካሞችን እና የአረጋውያን ቤት ለማደስ እያደረገ ያለውን ያላሰለሰ ጥረት በማድነቅ ለወደፊቱም አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠይቀዋል፡፡
የቤት ዕድሳቱ መርኃ ግብር ተጠቃሚ የሆኑ አረጋዊያን እና አቅመ ደካሞች በበኩላቸው ባንኩ በችግራቸው ጊዜ ደራሽ ሆኖ ስላገኙት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
Page 14 of 31